የጌታቸው ክህደት ፡- ከባንዳነት እስከ ተጠያቂነት



መግቢያ


በትግራይ ፖለቲካ የውጪ ጠላትና የውስጥ ክህደት የተለመደ ቢሆንም በዘመናዊ ትግራይ የባንዳ ክህደት ያጋጥማል ተብሎ ሊታሰብ አይገባም ነበር፡፡ የውጪ ጠላቶችን መክቶ ከሰላም ውጪ ማንበርከክ እንደማይቻል ያሳየው የትግራይ ህዝብ ከውስጥ የሚነሱ ባንዳዎችን ክህደት በማጋለጥ የህግ ተጠያቂ የሚያደርግበትንም ትግል የያድጋል፡፡ ለውጪ ጠላትም ብቻ ሳይሆን ለባንዳ ሴራም የማይነበረከከው የትግራይ ህዝብ አሁንም እነዚህን ባንዳዎች መታገሉን የሚቀጥል ነው፡፡ ይህንን ታሳቢ በማድርግ በዚህ አጭር ፅሑፍ የምናየው በትግራይ የምስለኔ መልክ ባለውና የአቶ ጌታቸው ረዳ ስብስብ የፈጠረውን ክህደት በማየት ከህግ አንፃር ተጠያቂ የሚሆንበትን ምክንያቶች ለመዘርዝር እንሞክራለን፡፡ 


በዝርዝርም የትግራይን ግዛታዊ አንድነት አሳልፎ ከመሰጠት፣ የህወሓትን የፖለቲካ አመራርና የሰራዊት አመራር ለማፍረስ የተደረጉ ክህደቶችን እንዲሁም ከተፈቃነቃይ ማስመሰልስና መልሶ መቋቋም አንፃርና የትግራይን የመደራደሪያ  አቅም ለማዳከም የሰራቸውን ክህደቶች በዚህ ፅሁፍ ለማሳየት እንሞክራለን፡፡ 


1) አቶ ጌታቸው ረዳ ክህደት የፈፀሙበት ዋናው የባንዳነት ተግባር የትግራይ መከላከያን ሆነ ብሎ በማኮላሸት የትግራይን ህልውና ሜዳ ላይ ማስጣት ነው፡፡ የዚህ የመጀመሪያ ክህደት ደግሞ ለራሱም የረጅም ጊዜ የትግል አጋር የሆኑ እና ለትግራይም ህልውና ሲታገሉ የነበሩ የትግራይ ሰራዊት አመራሮችን ማጥቃት ነው፡፡


የዚህ ድርጊት አላማ ደግሞ የትግራይን ወታዳራዊ አመራር በመምታት ሰራዊቱ እንዲበተን የማድረግ ትግራይ ወደፊት የሚቃጣባትን የህልውና አደጋ የምትመክትበትን የትግል አቅም ማዳከም ላይ ያለው ስትራቴካዊ ሴራ ነው፡፡


በዚህም እርምጃ ትግራይን ለጥቃት የተጋለጠች ፣ ለአገዛዝ የተንበረከከች በማድረግ በትግራይ ጥቅም ላይ መነገድ ለሚሹ የውጪ ጠላቶች ፍላጎት ማመቻቸት ፣ እነዚህንም የውጪ ጠላቶች የምትቋቋምበትን የትግል ቁመና ማፍረስና የድርድር አቅሟን ማዳከም ነው፡፡ 


2) ሌላው የአቶ ጌታቸው የክህደት ተግባር የትግራይን ህዝብ አንድነት መበታተንና የመሪ ድርጅቱን ህወሓትን የፖለቲካ አመራር መዋቅር ማፍረስ ነው፡፡


አቶ ጌታቸው የትግራይን ህዝብ ወክሎ የፕሪቶሪያን ውል የተዋዋለውን ህወሓትን ከተቻለ ማፍረስ ካልተቻለ ተዋካይ በማይሆንበት ደረጃ ማዳከም ፣ በዚህም የትግራይ ህዝብን ተደራዳሪ እንዳይኖረው ማድረግ እና የትግራይ ህዝብ አንድነትን በመበታተን ብሔራዊ ህልውና አደጋ ውስጥ የሚያስገባ የባንዳ ስራ ሲሰራ ቆይቷል፡፡


የጌታቸው ረዳ የትግራይ ተልዕኮ በአመራሩ መካከል መለያየትና በህዝቡም መካከል የፖለቲካ አለመራጋትን መፍጠር ሲሆን ማንኛውም የትግራይ ተወላጅም ይሁን አመራር በፕሪቶሪያ ላይ የሚኖረውን ወሳኝ ድርሻ መንጠቅ እና በትግራይ በኩል የፕሪቶሪ ስምምነት ባለቤት እንዳይኖረው ማድረግ ነው፡፡ 


በዚህም የውስጥ መቃቃርን በመፍጠር የአመራር አንድነትን በማፍረስ ከዚህ አልፎም በህዝቡ መካከል ያለውን አንድነት በመሸርሸር የትግራይን የመደራደር አቅም በማዳከም ለፌዴራል ላኪዎቹ ፍላጎት ተንበርካኪ ማድረግ ነው፡፡


3) ዋናው የአቶ ጌታቸው ረዳ የባንዳነት መገለጫ ደግሞ የትግራይን መልሶ መቋቋም ፣ ግዛት ማስመለስና ተፈናቃዎችን ወደ መኖሪያ ቀያቸው የመመለስ አገራዊ አጀንዳ ላይ የፈፀመው ክህደት  ነው፡፡ 


አቶ ጌታቸው በጊዜያዊነት ቢሆንም በነበረው የማስተዳደር ስልጣን ዋንኛው ተግባሩ የነበረው የትግራይ ግዛት ማስከበር ተፈናቃይ መመለስ እና መልሶ ማቋቋም ቢሆንም ይህንን ዋንኛ ተግባሩን እርግፍ አድርጎ ትቶ ጊዜውን ያሳለፈው ፋይዳ የሌለው ተራ ንትርክ ላይ ነው፡፡ በዚህም በትግራይ መሰረታዊ ጥቅም ላይ ተደርድሯል ወይም ክህደት ፈፅሟል በሚያስብል መልኩ ተፈነቃዮች ወደቀያቸው እንዳይመለሱ አድርጓል፣ የግዛት አንድነት እንዳይረጋገጥ እና መልሶ መቋቋም እንዲሰናከል አድርጓል፡፡ 


በዚህ መልኩ የተፈፀመውን ክህደት ከባድ የሚያደርገው ደግሞ እነዚህ ወሳኝ የተፈቃናይ ወደ ቀዬ የመመለስ ጥያቄዎችን እንዲደበዝዙና በሂደት እንዲጠፉ በማድረግ የተሰራው ሴራ ሲሆን በዚህ ምትክ የፌዴራል መንግስት ስልጣን የሚያጠናክር ስራ ሰርቶ የማለፍ የባንዳ ተግባር ነው ፡፡ 


4) አቶ ጌታቸው ወደ አምባገነንነት የስልጣን ዘመናቸው ሲቃረቡ የፈፀሙት ሌላው ክህደት ከጠላት ጋር በመተባበር የሚነሳባቸውን ተቃውሞ ማፈን ነው፡፡


ክህደቱ የትግራይ መሪዎችና ተወላጆች የሚያቀርቡትን ቅሬታና አቤቱታ ለማፈን ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር እጅና ጓንት ሆኖ ሰርቷል፡፡ 


የፕሪቶሪያ ስምምነት ደካማ አፈፃፀም አለመቃወሙ እንደተጠበቀ ሆኖ እነዚህን ድክመቶች የሚታገሉ የትግራይ ወላጆችን እና መሪዎችን ሊህቃንን እያሳደደ ጫና በመፍጠር የፌዴራል መንግስት ተጠያቂ የሚሆንበትን ህጋዊና ፖለቲካዊ አግባብ ተድበስብሰው እንዲጠፉ አድርጓል፡፡


በመሆኑም፡- ከላይ የተዘረዘሩት ፖለቲካዊና ህጋዊ ምክንያቶች አቶ ጌታቸው ረዳ በባንዳነትና በአገር ክህደት የሚያስጠይቁ በመሆናቸው ለዚሁ ተጠያቂ ማድረግ የሚያስችል አሰራር መስፈን አለበት፡፡ በዚህ መሰረት የሚከተሉት እርምካዎችን በአፋጣኝ እንዲወሰዱ አስፈላጊ ሆኖ ሊገኝ ይችላል፡፡ 


1.      በትግራይ ላይ የፈፀሙትን የሀገር ክህደት ወንጀል በአስቸኳይ በቁጥጥር ስር አውሎ ለህግ ማቅረብ።


2.      ከጠላት ሃይሎች ጋር በመተባበር እና የትግራይን የመከላከያ ስርዓት በማፍረስ ላይ ስላለው ሚና ይፋዊ ምርመራ ማድረግ


3.      የትግራይ ተወላጆች ወደነበሩበት መመለስ እና የተፈናቀሉ የትግራይ ተወላጆች እንዳይመለሱ በማደናቀፍ ሙሉ ህጋዊ ተጠያቂነት።


4.      ህጋዊነትን በመሻር እና ወደፊት በትግራይ ውስጥ ምንም አይነት የመሪነት ሚና እንዳይኖረው የሚከለክለው መደበኛ የፖለቲካ ውሳኔ


5.      የትግራይን ትግል ለማደናቀፍ የተጫወተውን ሚና ለመጪው ትውልድ ለማስታወስ ክህደቱን የሚዘግብ የታሪክ መዝገብ።


መደምደሚያ ፡- የአቶ ጌታቸው ረዳ ክህደት ፖለቲካዊ ብቻ ሳይሆን በትግራይ ህልውና ላይ የተፈፀመ የሰቆቃ ተግባር ነው። ሆን ብሎ የሕወሓትን አመራር ማፍረሱ፣ የትግራይን የፖለቲካ አንድነት በመበጣጠስ የተጫወተው ሚና፣ የተያዙ ቦታዎችን ለማስመለስ ፈቃደኛ አለመሆኑ፣ የተፈናቀሉ የትግራይ ተወላጆችን አሳልፎ መስጠቱ በከፍተኛ የሀገር ክህደት ወንጀለኛ ያደርገዋል፡፡ 


ከዚህ በተጨማሪ የራሱን ህዝብ መስዋዕት አድርጎ የውጭ ሃይሎችን ለማገልገል በግልፅ ያሳየው የክህደት ተነሳሽነት  ከባድ የህግ እና የታሪክ መዘዞች ሊገጥመው ይገባል፡፡ የትግራይ ህዝብ እንዲህ አይነት ባንዳ ሳይቀጣ እንዲቀር በፍጹም መፍቀድ ለሚመጣው ትውልድ ብልሹ ባህልን ማውረስ ነው፡፡

Comments

Popular posts from this blog

Getachew Reda: The Ultimate Traitor—A Case for High Treason Against Tigray’s Betrayer

ድምጽ-አልባው ዘረፋ፡- በጦርነት ለደቀቀው ህዝብ የፈጠረው ተጨማሪ ችግር