የጌታቸው የሽንፈት ድምጾች በኢትዮፎረም

ሰሞኑን ኢትዮፎረም የራሱ ያልሆኑ ድምጾችየሚስተጋበት የገደል ማሚቶ ሆኖ እያገለገለ ነው፡፡ አቶጌታቸው አክቲቪስት ሆነው በአደባባይ በየ-ዩቱዩቡ ያሰራጩትአሉባልታ አልበቃ ሏቸ አሁን ደግሞ በታዋቂ ዩቱዩብ ጀርባብቅ ያሉ ይመስላሉ፡፡ ቀድሞ ከትግራይ ህዝብ ጎን ተስልፎድምጹን ሲያሰማ የምናውቀው ኢትዮፎረም አሁን ደግሞ በትግራይ ህዝብ እና በመሪው ድርጀት ላይ የተነሳ ይመስላል፡፡ በሚንስተነት ማዕረግ የምስራቅ አፍሪካ አማካሪ ሆነውተሾሙ የተባሉት አቶ ጌታቸው የምስራቅ አፍሪካ አማካሪ ሆኖ መሾም ማለት ትግራይን መበጥበጥ እንደሆነ የትግራይንጉዳይ አልጨረስኩም በሚል ሰጡት አሳብ ነግረውናል፡፡

 


አቶ ጌታቸው ማልያ ቀይረው ፣ በአዲስ ለተሰለፉበት ሜዳሊጫወቱ ፣  በኢትዮፎረም ጀርባ ያስተጋቡትን ድምፅ ከንቱጩኸት ሆኖ ቢገኝም የሚናቅ ግን አይደለም፡፡ እናም አልፎአልፎ የተወሰነውን አይተነዋል፡፡ 


ኢትዮፎረም ከወገንተኝነት ድተው አስተያየት የሰጡኝላቸው በግልጽ ስማቸው እነአቶ ጌታቸው ናቸው፡፡ ምክንያቱምየቀረበው አመክንዮ በአብዛኛው የተሸናፊዎች ድምጽ ነው፡፡ 

ጦርነቱን ከብልጽግና ወደ ህወሓት በማምጣት ፣ ወንጀሉን  ከገዳይ ወደ ሟች ፣  ዳይ እየተከላከሉ ተበዳይተበዳይን የወቀሱበት የሚስተዛዝብ አሳብ ነው፡፡ ይህ ቀደምብለውም መቀለ እያሉ ችግሩ የእኛ ነው በሚል ወደ ህወሓትለማላከክ ያደርጉት የነበረው ጥረት ተቀጥያ ነው፡፡ 


ድሮ ድሮ አለቃቸው አብይ አህመድ ኢህአዴግን ሊያፈርሱሲሉ መጀመሪያ ያደረጉት ኢህአዴግን በአደባባይ ማንቋሸሽመሆኑን እናስታውሳለን፡፡ 27 አመት ጨለማ ነበር፣ ኢህአዴግአሳሪ ነበር ፣ እንደዚህ ነበር ፣ እንደዚያ ነበር እያሉ ኢህአዴግንሲኮንኑ ቆዩ በኋላ ኢህአዴግን አፈረሱት፡፡ እነ አቶ ጌታቸውምመቀለ እያሉ ጥፋትን ወደ ህወሓት ያላክኩ ነበር፡፡ አሁንኢትዮፎረም ላይ እየሰማነው የነበረውም ጦርነቱን ወደህወሓት የማላከክ አባዜ ብልጽግናን ከተጠያቂነት ነፃ አድርጎ ህወሓትን የማፍረስ ጅማሬ መሆኑ ገብቶናል፡፡ 


አቶ ጌታቸው ደብረፅዮን ጥላልኝ ፣ ህወሓትን አንቋሽልኝለው ለኢትዮፎረሞች የነገራቸው ነው የሚመስለው ፡፡ ህወሓትን በማስረዳትም በመረዳትም ልክ ነው ብሎ ስህተትመንቀስ ምን የሚሉት ነው?ህወሓት ከአዲስ አበባ መምጣትአልነበረበትም፣ስልጣን ለኦሮሞ መስጠት አልነበረበትም እያለንያለው ከእነሽመልስ አብዲሳ ጋር የሚለው አቶ ጌታቸው ነው ፡፡ 


አቶ ጌታቸው በኢትዮፎረም አብሮ ያቦካውን እነሱ ብቻይጋግሩት የሚል ነው የሚመስለው ያሉ አሳብ ሰጪዎች ይሄ ሁሉችግር ላይ ጌታቸውም ነበረበት የሚሉ አሉ፡፡ እናም የምስራቅአፍሪካ ጉዳይን የማማከር ስራ ትግራይን ከማተራመስ ሙከራተጀምሯል፡፡ ይሳካል አይሳካም የሚለው ጊዜ የሚፈታውይሆናል፡፡ እኛም አውቀናል ጉድጓድ ምሰናል እንደሚባለውበኢትዮፎረም የተሰማው ጩኸት የማን እንደሆነ ገብቶናል፡፡ 


Comments

Popular posts from this blog

Getachew Reda: The Ultimate Traitor—A Case for High Treason Against Tigray’s Betrayer

ድምጽ-አልባው ዘረፋ፡- በጦርነት ለደቀቀው ህዝብ የፈጠረው ተጨማሪ ችግር

የጌታቸው ክህደት ፡- ከባንዳነት እስከ ተጠያቂነት